"ከሁሉ የሚበልጠው ኢንቨስትመንት የነገ ሃገር ተረካቢ የሆነ ተማሪዎቻችን ላይ መስራት ነው።"

12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ሽልማት ሰጥተናል።

2014 የትምህርት ዘመን ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 896,520 12 ክፍል ተማሪዎች መካከል በሃገር አቀፍ ደረጃ 600 በላይ ያመጡ ተማሪዎች ቁጥር 273 ሲሆን ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል 125 ተማሪዎች ከአዲስ አበባ ከተማ ናቸው። በሃገር አቀፍ ደረጃ ፈተና ከወሰዱት ውስጥ ያለፉት 3.3% ሲሆኑ እንደ አዲስ አበባ 19.8 % ናቸው።

ያሰብነው ውጤት ባይመጣም ዛሬ የሸለምናቸው በፈተና ውስጥ ያለፋ እንቁዎች ስለሆኑ ነው።

ገና ብዙ መስራት የሚጠበቅብን በመሆኑ በቀጣይ ከዚህ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የትምህርት ባለድርሻ አካላት፣ መምህራን፣ ወላጆች እንዲሁም ተማሪዎች የበኩላችሁን አስተዋጽዖ ልትወጡ ይገባል

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!!

ከንቲባ / አዳነች አቤቤ

Share this Post