የከተማችን ነዋሪዎች አንገብጋቢ ጥያቄ የሆነው የመኖሪያ ቤት አቅርቦት በመንግስት ብቻ የሚመለስ ሳይሆን ከግሉ ዘርፍ ጋር በትብብር መስራትን እና የግሉን ዘርፍ ማበረታታትን ይጠይቃል።

ዛሬ የከተማችን የመኖሪያ ቤቶችን በመገንባት ለህብረተሰቡ በማቅረብ ላይ የሚገኘው ኖህ ሪል ስቴት የገነባቸው 754 መኖሪያ ቤቶች ተመርቀዋል።

ባለፉት 5 የለውጥ ዓመታት የተገነቡ 5000 ቤቶችን ጨምሮ እስከአሁን ከ8600 በላይ ቤቶችን ገንብቶ ለነዋሪዎች ያስተላለፈ ሲሆን፣ ግንባታቸው በመጠናቅቅ ላይ ያሉ ቤቶች በጥራት መገንባታቸውን እና የበርካታ ነዋሪዎችን የቤት ችግር የሚቀርፉ መሆናቸውን በጉብኝታችን ወቅት ተመልክተናል።

ለከተማችን ዕድገትና ለህዝባችን ፋይዳ ያላቸው በመሆኑ በመኖሪያ ቤት ላይ ለተሰማሩ ኩባንያዎች የከተማ አስተዳደራችን ድጋፍ ማድረጉን ይቀጥላል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Share this Post