ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች የትራንስፖርት አገልግሎትን ለማዘመን እና በዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመቅረፍ ዘመናዊ የትራንስፖርት ስርዓት መዘርጋት በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል።

 

ከንቲባ አዳነች በውይይቱ ወቅት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በቅርበት እና በተናበበ መንገድ በመስራት በዘርፉ ያለውን ክፍተት በዘላቂነት ለመፍታት የከተማ አስተዳደሩ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር አለሙ ስሜ በበኩላቸው ሚኒስቴር መስሪያቤቱ በከተማዋ ያለውን የትራንስፖርት እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍ እና ዘመናዊ የከተማ ሎጂስቲክ ስርዓትን ለመዘርጋት ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰው ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያካተተ የሎጂስቲክ ካውንስል በማቋቋም ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት እየሰራ እንደሆነም ተናግረዋል።

ለተጨማሪ መረጃ፦

👉 YouTube https://www.youtube.com/channel/UCagI4q5d_EtvTsajRXWnFjA

👉 Tik Tok https://www.tiktok.

👉 Telegram https://t.me/AAcommu

👉 Facebook https://www.facebook.com

👉 Website https://cityaddisababa.gov.et/

Share this Post