"የዘመነ የንግድ ስርዓት፣ ለላቀ ገቢ እድገት!"

------------

በተቀናጀና ንቁ የህዝብ ተሳትፎ በከተማችን ፍትሃዊ እና ዘመናዊ የንግድ ስርዓት እናሰፍናለን!’  

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች " የዘመነ የንግድ ስርዓት፣ ለላቀ ገቢ እድገት!" በሚል መሪ ሀሳብ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር የውይይት መድረክ ተካሂዷል፡፡

በንግዱ ዘርፍ የታዩ ለውጦችና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና የመድረኩ ዋና የውይይቱ አጀንዳ ሲሆን ሀገራችን እና ከተማችን ባስመዘገቡት ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ስኬቶች እና እያጋጠሙ ባሉ ፈተናዎች ዙሪያ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል።

 የንግዱ ማህበረሰብ አስተዳደሩ ያስቀመጣቸውን ዋና ዋና ግቦች ለማሳካት እንቅፋት የሆኑ ተግዳሮቶችን በመገንዘብ ችግሮቹን ለመፍታት በሚደረገው ጥረትም የበኩላቸውን አስተዋፆኦ ለማበርከት ከምንም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡

ህግንና ሥርዓትን አክብረው የሚነግዱ ነጋዴዎች በሀገር ልማት ላይ ያላቸውን አዎንታዊ ሚና በተገቢው በመገንዘብ ህገወጥ ንግድን በመከላከል ላይ የድርሻቸውን ሚና እንዲጫወቱም መልዕክት ተላልፏል፡፡

Share this Post