03
Jan
2024
በጉብኝታቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ታላቁ የዓድዋ ድል አባት አርበኞች የብሔርና የዕምነት ልዩነት ሳይገድባቸው ለሀገር ሉዓላዊነትና ነጻነት በአንድነት የመቆማቸውን ታሪክ የወል ትርክት በማድረግ ትውልድ እንዲማርበት ሙዚየሙ መገንባቱ ሌላ ታላቅ ታሪክ መሰራቱን ከንቲባ ጎሹ ገልጸዋል::
ከጉብኝቱ በኃላ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የባህርዳር ከተማ አመራሮችን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው የተወያዩ ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አመራር በመናበብ እና በመቀናጀት በርካታ ሰው ተኮር ስራዎችን እንዲሁም የከተማዋን ገፅታ የቀየሩ እና አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለአገልግሎት ክፍት በማድረግ ላይ እንደሚገኝ በውይይቱ ወቅት ተናግረዋል::