በአዲስ አበባ የሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ዓድዋ ዜሮ ዜሮ ኪ/ሜ ሙዚየምን ጨምሮ በከተማችን ተገንብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ ትላላቅ ፕሮጀክቶችንና ሰው ተኮር ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል::

የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮቹ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማውን ነዋሪ የኑሮ ጫና ለማቅለል እየሰራቸው ያሉ ስራዎች የበርካቶችን ሕይወት እየቀየሩ መሆናቸውን መገንዘባቸውን ገልፀዋል:: የዓድዋ ዜሮ ዜሮ ኪ/ሜ ሙዚየምን ጨምሮ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባሻገር ለትውልድ የሚተላለፉ ስራዎች መሆናቸውንም የተፎካካሪ ፖርቲ ተወካዮቹ ተናግረዋል::

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው የከተማ አስተዳደሩ የነዋሪውን ሕይወት በዘላቂነት ለመቀየር ፣ ከተማዋን ለኑሮና ለስራ ምቹ ለማድረግ እንዲሁም የከተማችንን ገፅታ የሚቀይሩ በርካታ እቅዶችን ከነዋሪው ጋር በጋራ እየመከረ በመተግበር ላይ ይገኛል ብለዋል::

ለተጨማሪ መረጃ፦

👉 YouTube https://www.youtube.com/channel/UCagI4q5d_EtvTsajRXWnFjA

👉 Tik Tok= https://www.tiktok.com/@aacommu

👉 Telegram https://t.me/AAcommu

👉 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=100066583024934&mibextid=ZbWKwL

 

👉 Website https://cityaddisababa.gov.et

Share this Post