"ዛሬ ከቻይናዋ የቾንቺን ከተማ አስተዳደር ኮንግረስ ሊቀመንበር ዣዎ ሺቺንግ ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነት በሚጠናከርበት ጉደይ ዙሪያ ተወያይተናል።

የቾንቺን ከተማ አስተዳደር ኮንግረስ ሊቀመንበር ዣዎ ሺቺንግ እና የልዑካን ቡድናቸው አዲስ አበባ ከበርካታ የቻይና ከተሞች ጋር በቅርበት እንደምትሰራ አስታውሰው፣ ከቾንቺን ከተማ ጋርም የእህትማማችነት ስምምነት እንድንፈራረም እና ግንኙነታችን ይበልጥ እንዲጠናከር ያላቸውን ፍላጎት መነሻ በማድረግ በኢኮኖሚ ትብብር፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በቴክኒክና ሞያ፣ በነፃ የትምህርት እድል እንዲሁም በባህልና ቱሪዝም ዘርፎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የእህትማማችነት ስምምነት ለመፈራረም ተስማምተናል።"

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Share this Post