08
Jan
2023
ከ3.1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት የሚካሄድ ይህ ግንባታ ሁለንተናዊ ስልጠናና ክህሎት የሚሰጥበት የማሰልጠኛ ማዕከል ያለው ሲሆን ሴቶች በስነልቦናና በክህሎት ብቁ ሆነው እንዲወጡ ያስችላል።
ግንባታው የስልጠና ክፍሎች ፣የማደርያ ዶርሚተሪ ፣ የህፃናት ማቆያ ፣የመመገብያ ክፍሎች ፣መዝናኛዎች እና ሱቆች እንዲኖሩት ታስቦ የተሰራ ሁለገብ ማዕከል ነው፡፡
ሴቶች የማህበረሰብ መሰረት ናቸው ፤በማህበረሰቡ ውስጥ ስር በሰደዱ የተዛቡ አስተሳሰቦች እና ችግሮች ምክንያት ከሚያጋጥማቸው ማህበራዊ እክሎች በማላቀቅ ጠንካራ ማህበረሰብንና ትውልድን የመገንባት ስራ አንድ አካል ነው፡፡
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን አብዝቶ ይባርክ!!