ባለፉት 12 ዓመታት የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ከ4.3 ቢሊዮን ብር በላይ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ድጋፍ ማድረጋቸዉ ተገለጸ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ባለፉት 12 አመታት 4.3 ቢሊዮን ብር በላይ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ድጋፍ ማድረጋቸዉን የአዲስ አበባ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት /ቤት አስታወቀ፡፡

2003 እስከ 2010 . ድረስ ለግድቡ 1.1 ቢሊዮን ብር እንዲሁም 2011 እስከ 2015 . ባሉት ዓመታት 3.2 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት /ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ምስክር ነጋሽ ገልፀዋል፡፡

12 አመቱ ላይ የሚገኘው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 2015. ብቻ በአዲስ አበባ ከተማ 685 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ እስከያዝነው መጋቢት ወር ድረስ ብቻ 427 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡንም ዋና ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡

እንደ ሃገር 60 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ የተገለፀ ሲሆን ሰፊው ድጋፍ የሚጠበቀው ደግሞ ከአዲስ አበባ ከተማ በመሆኑ ግንባታው ሙሉ በሙሉ እስኪጠናቀቅ ድረስ 11 ዱም ክፍለ ከተማ ሰፊ የንቅናቄ መድረክ በማድረግ ገቢ የማሰባሰብ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የግንባታ ደረጃ አሁን ላይ 90 በመቶ መድረሱም ተገልጿል፡፡

የከተማዋ ነዋሪዎች እና ባለድርሻ አካላት እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ ቀርቧል፡፡

Share this Post