"እንኳን ለ18ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን!" ከብሔር ብሔረሰቦች ዋና ከተማ-አዲስ አበባ

 

--------

አንዳችን የአንዳችን አካል ፣ አንዳችን የሌላችን ሃሳብና ጉልበት ሆነን ብዝሃነትን እና እኩልነትን በስራ አረጋግጠን የወደፊቷን ኢትዮጵያን እንገነባለን።

ዛሬ በጂግጂጋ ከተማ ያየነውም ይሄንኑ የሚያጠናክርልን ነው:: ወርቃማዋ ጂግጂጋ የአንድነታችንና እኩልነታችን መሰረት የሆነውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀንን ስታከብር በድምቀት ፣ ተስፋን በሚያጭር ፣ የያዝነውን የብልፅግና ጉዞ እውን በሚያደረግ ፣ በሚያነሳሳ እና በሚያነቃቃ መንገድ መሆኑ በዓሉን ለየት ያደረገዋል።

ለጋራ ብልፅግና የተጋመደው ውጥናችን ፣ በጋራ ቃል ኪዳናችን እያፀናን ፣ እኩልነት እና አንድነትን በፅኑ መሰረት ላይ በመገንባት የኢትዮጲያ ልጆች ብልፅግናን እናረጋግጣለን!

በድጋሚ እንኳን አደረሳቹ አደረሰን !!

Share this Post