04
Nov
2022
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ 18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ተፈራ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ቢሮው ባለፉት ሦስት ወራት 17 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ ከ 18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የእቅዱ 106 ነጥብ 8 በመቶ በላይ ማሳካት ችሏል፡፡
አፈጻጸሙ ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ33 ነጥብ 7 በመቶ መጨመሩን አስታውሰው፤ በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው አጠቃላይ ገቢ የ26 ነጥብ 5 በመቶ የሚሸፍን መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ገቢ ግብርን ለማሳደግ ብሎም አዳዲስ የገቢ አማራጮችን ለማስፋትና በዘላቂነት እየተሰራ ነው ተብሏል ።