ታህሳስ 22 2016 አዲስ አበባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሌላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሂ አብዲ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ታሪካዊ የሆነ የምግባቢያ ሰንድ ፈርመዋል።

የኢፌድሪ መንግስት እና የሶማሌላንድ መንግስት የፈረሙት የትብብር እና የአጋርነት መግባቢያ ሰነድ በተለያዩ ዘርፎች በቀጣይ ለሚኖር ግንኙነታቸው ማዕቀፍ የሚሆን ነው። ይህ የመግባቢያ ሰነድ የኢትዮጵያን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት እውን የሚያደርግ፣ የባህር በር አማራጮችን የሚያሰፋ፣ የሁለቱን ወገኖች የፖለቲካ፣የዲፕሎማሲ፣ የፀጥታ እና የኢኮኖሚ ትብብር የሚያጠናከር ነው።

እንዲሁም ሰነዱ በፖለቲካ እና በዲፕሎማሲ ዘርፍ የሚኖራቸው ግንኙነት የሚጎለብትበትን አካሄድ የሚያካትት ነው። ይህ የመግባቢያ ሰነድ የኢትዮጵያ መንግስት በሰጥቶ መቀበል መርህ እና ለጋራ ጥቅም ከጎረቤቶቿ ጋር የመስራት ፍላጎት እና አቋሟን መልሶ የሚያፀና ነው። ይህ ሰነድ አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እና ለአፍሪካ ቀንድ ትሥሥር የላቀ ፋይዳ ያለው ነው። እንዲሁም ሰነዱ ኢትዮጵያ በቀጠናው ሰላም እና ደህንነት የሚገባትን ሚና እንድትጫወት የተሻለ እድል የሚፈጥር ነው።

ለተጨማሪ መረጃ፦

👉 YouTube https://www.youtube.com/channel/UCagI4q5d_EtvTsajRXWnFjA

👉 Tik Tok= https://www.tiktok.com/@aacommu

👉 Telegram https://t.me/AAcommu

👉 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=100066583024934...

👉 Website https://cityaddisababa.gov.et

Share this Post