በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ 24 የስፖርት ማዘውተሪያዎችንና የልጆች መጫወቻ ማዕከላት ተመርቀው ለገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

ፕሮጀክቶቹ 410,217,800.ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው ሲሆን፣ 24 ፕሮጀክቶች 7 በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር / አብይ "የመደመር ትውልድ" መፅሐፍ ሽያጭ በተገኘ ገቢ ለከተማችን ህፃናትና ወጣቶች የስፓርት ማዘወተሪያ ለመገንባት የተከተማ አስተዳደሩ ቃል ገብቶ የተረከበው ናቸው።

ጠቅላ ሚኒስትሩ አዲስ አበባን ለዛሬና ለነገው ትውልድ ምቹ ለማድረግ፣ በከተማችን ልጆች እንደ ልባቸው የሚቦርቁባት በየአካባቢያቸው በቂ የመጫወቻ እና ስፖርት ማዘውተሪያ ቦታ እንዲኖራቸው ለማድረግ ባበረከቱልን "የመደመር ትውልድ" መፃሀፍ ለከተማ አስተዳደሩ አደራ ሰጥተው በሦስት ወር ጊዜ ውስጥ 7ቱን የወጣት የስፖርት ማዘውተሪያ እና የህፃናት መጫወቻ 110 ሚሊዮን ብር "ከመደመር ትውልድ" መፅሃፍ ሽያጭ በተገኘ ገንዘብ ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

ሌሎቹ 17 ፕሮጀክቶች ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ 300 ሚሊዮን በላይ በሆነ ወጪ ተደርጎባቸው የተገነቡ ሲሆን፣ ይህም የከተማው ወጣቶችና ልጆች በአካል እና በአእምሮ የበለጸጉ ሆነው እንዲያድጉ ለማድረግ ከተማ አስተዳደሩ በትኩረት ለመስራቱ ማሳያዎች ናቸው።

Share this Post