"ዛሬ በአዲስ ከተማ የተመረቁት 3የዳቦ ፋብሪካዎች በጥቅሉ በከተማችንን ዕለታዊ የዳቦ ማምረት አቅም ወደ 5.2 ሚልየን የሚያሳድጉ ናቸው" (ከንቲባ አዳነች አቤቤ)

ዛሬ ለከተማችን ነዋሪዎች ተጨማሪ ብስራት የሆኑ 3 የዳቦ ፋብሪካዎችን መርቀን አገልግሎት አስጀምረናል።

የዳቦ ፋብሪካዎቹ በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የከተማችን ነዋሪዎች ኑሮ በመደጎም ረገድ ትልቅ ድርሻ የሚኖራቸው ሲሆን በቀን እስከ 1 ሚልየን ዳቦ ያመርታሉ። በጥቅሉ በከተማችን ዕለታዊ የዳቦ ማምረት አቅምን ወደ 5.2 ሚልየን የሚያሳድጉ ናቸው።

የዳቦ ፋብሪካዎችን ከአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር ገንብታችሁ ለአገልግሎት ያበቃችሁ አልኸይር የዳቦ ፋብሪካን ዩኒቲ የዳቦ ፋብሪካን እና ዮናን የዳቦ ፋብሪካን በከተማችን ነዋሪዎች እና በተጠቃሚዎች ስም ላመሰግን እወዳለሁ።

Share this Post