ይቻላል! በ90 ቀናት የለሚ ኩራ ክፍለከተማን አገልግሎት ወደ ዲጂታል ቀይረናል::

6 ባለ አራት ወለል የሆኑ 240 ቤቶችን ገንብተናል:: የረዥም ግዜ የመሰረተ ልማት ጥያቄ ላለባቸው የአርሶአደር የመኖሪያ አከባቢዎች የውሃ የመብራት እንዲሁም ሌሎች መሰረተልማቶችን ገንብተን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል::

ቅድሚያ ህዝቡን በሙስና ያስመረሩትን አካላት በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ሌብነትን ለማስቀረት እና አገልግሎት አሰጣጡ ከተማውን በሚመጥን ደረጃ እንዲሆን የዲጂታል አገልግሎት የሚሰጥ የአስተዳደር ህንፃ ገንብተን ዛሬ ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል::

በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ ነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ባለሃብቶችን በማስተባበር 6 ባለ አራት ወለል የሆኑ 240 ቤቶችን ገንብተን ለአከባቢው ነዋሪዎች አስረክበናል::

የረዥም ዘመን የመሰረተ ልማት ጥያቄ ላለባቸው የአከባቢው አርሶአደሮች የውሃ የመብራት እንዲሁም የሌሎች መሰረተ ልማቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑም አስችለናል::

ህዝብን ለማገልገል ከመጣን በሌሎች ደባል ፍላጎቶች ሳንያዝ የህዝባችንን ጥያቄ ደረጃ በደረጃ በመመለስ ለመኖር ምቹ የሆነች ከተማ ለመገንባት እንሰራለን:: ይህ ብዙዎችን ተጠቃሚ ያደረገ ፕሮጀክት እንዲሳካ ማህበራዊ ግዴታቸውን ለተወጡ የከተማችን ባለሃብቶች በነዋሪዎች ስም ምስጋናዬን ላቀርብ እወዳለሁ::

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን አብዝቶ ይባርክ!!

ከንቲባ / አዳነች አቤቤ

Share this Post