በአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር አዘጋጅነት በወዳጅነት አደባባይ ለትዉልደ ኢትዮጵያን በተካሄደው የእንኳን ደህና መጣችሁ የአቀባበል መርሐ ግብር ላይ ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ያስተላለፉት መልዕክት ።

 

* ዳያስፖራው የሀገሩን ክብር ለመጠበቅ በዓለም አደባባይ የተጫወተው የአምባሳደርነት ሚና ከፍተኛ ነው ፤

* ዳያስፖራው ለእናት ሀገሩ ጥሪ የሰጠው ምላሽ አኩሪ መሆኑን እና ያሳየው ፅናትም ማሸነፍን ከነ ሙሉ ክብሩ የሚያጎናፅፍ የአንድነት ካባ ሆኖ የሚታይ ነው ፤

* ኢትዮጵያን ለማፍረስ የተባበሩት የውስጥ እና የውጭ ኃይሎች የተለያዩ ጫና ቢያደርጉም በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ፣ “#NoMore” /በቃ/ ብለው በያሉበት ሀገር ያሰሙት ድምፅ ከኢትዮጵያ አልፎ የመላዉ አፍሪካውያን ንቅናቄ ሆኗል ፤

* ስለ ዳያስፖራ ሲነሳ መሪዎቹን ማሸማቀቅ እና የፖለቲካ ሽኩቻ ማሳያ መሆኑ ዛሬ ላይ ታሪክ ሆኗል ፤

* ባይተዋርነት ነግሶ ኢትዮጵያውያን እዚህ እና እዚያ ሆነን መራራቃችን ቀርቷል ፤ ይህ ደግሞ በታሪካችን አዲስ ምዕራፍ ነው ፤

* ኢትዮጵያ የተሠራችበት ውቅር ከቃል በላይ ነው ፣ ለእርሷ የተሰጠ በልጆቿ ደም ውስጥ ብቻ ያለ ከሌሎች ዓለም ሁሉ የተለየ አንዳች ልዩ ፀጋ አላት ፤

* ኢትዮጵያ ትፈርሳለች የሚለውን ብሂል ልጆቿ አፍርሰውታል ፤ በጀግንነት እየወደቁ ቀና ማለትን አሳይተናል ፤ ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት አሸንፋለች ፤

* አዲስ አበባም እንደተሟረተባት ሳይሆን ሰላም መሆኗን በግልጽ እያሳየች ነዉ ፤

* ዳያስፖራው በሀገሩ በሚያደርገው ቆይታ የሀገሩን ምርት እንዲገዛ እና የበኩሉን ሚና እንዲጫወት አደራ እላለሁ ፤

* ኢትዮጵያ የምትበለጽገው በልጆቿ ጥረት በመሆኑ ሁላችንም በጋራ ልንቆም ይገባል ፤ ብለዋል ።

Share this Post