አዲሱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የካቢኔ አባላትን በመሾም ተጠናቀቀ ።

በዛሬው እለት ምስረታውን በይፋ ያካሄደው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የካቢኔ አባላትን ሹመት በማጽደቅ ተጠናቋል ።

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የካቢኔ አባላትን ለምክር ቤቱ ያቀረቡ ሲሆን ምክር ቤቱም በቀረቡ እጩዎች አስተያየት በመስጠት አጽድቋል ።

የቀረቡት እጩዎች የረዥም ጊዜ የስራ ልምድ፣የትምህርት ዝግጅት እና በመሩት ተቋማት ውጤታማ አፈጻጸም የነበራቸው መሆኑን ተገልጿል ።

በተጨማሪም ከተለያዩ ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርዎች የተካተቱበት ካቢኔ እንዲሆን ተደርጓል ።

በዚሁ መሠረት፦

1.ዶ/ር ቀነአ ያደታ የሰላምናጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ

2.ዶ/ር ሂሩት ካሳው የባህል፤ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ

3.ወ/ሮ ጽዋዬ ሙሉነህ የፍትህ ቢሮ ኃላፊ

4.አቶ ጀማል አሊዬ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ

5.አቶ ዳዊት የሺጥላ የትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ

6.ኢ/ር ሀያልነሽ ሀብተማሪያም የዲዛይን እና ግንባታ ቢሮ ኃላፊ

7.ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱ የቴክኒክ ሙያ ፣ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ

8.ዶክተር ዮሃንስ ጫላ የጤና ቢሮ ኃላፊ

9.አቶ አደምኑር ዋበላ የንግድ ቢሮ ኃላፊ

10.አቶ ዘላለም ሙላቱ የትምህርት ቢሮ ኃላፊ

11.ዶ/ር ሀና የሺንጉስ የሴቶች ፣ህጻናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ

12.አቶ ሙሉጌታ ተፈራ የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ

13.አቶ አብረሃም ታደሰ የወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ

14.አቶ ዮናስ ዘውዴ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ

15.ወ/ሮ ጽጌሬዳ ወርቁ የከተማ ውበት እና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ

16.ዶ/ር ዳዲ ወዳጆ የፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር

17.አቶ ግርማ ሰይፉ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር

18.አቶ ዩሱፍ ኢብራሂም ሽፈራው የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን በመሆን ተሹመዋል።

Share this Post