09
Nov
2021
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሀገር መከላከያን እና አሸባሪው የህውሃት ቡድን በከፈተው ጦርነት የተፈናቀሉ ዜጎችን ለማቋቋም ማምሻውን በተካሄደው የገቢ ማሰባሰባ መርሐግብር 1 ቢሊዮን 540 ሚሊዮን 732 ሺህ ብር መሰብሰብ ተችሏል።በሸራተን አዲስ ሆቴል በተካሄደው የገቢ ማሰባሰብ መርሐግብር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ፣የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰራዊት ግንባታ ስራዎች አስተባባሪ ሌተናል ጀነራል ባጫ ደበሌ፣ የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሚንስትር ዶ/ር አብረሃም በላይ፣ የሀይማኖት አባቶች እና ባለሃብቶች ተሳትፈዋል ።
በአንድ ጀምበር ከተሰበሰበው ከ1.ቢሊዮን 540 ሚሊዮን 732 ሺህ ብር የኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር 1 ቢሊዮን 23 ሚሊዮን 581ሺህ ብር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ቀሪውን በከተማዋ የሚገኙ ባለሀብቶች ፣ የተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ግለሰቦች ናቸው