የሰንደቅ ዓላማ ቀን በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ ተከበረ።

 

"በአዲስ ምዕራፍ በተሟላ ሉዓላዊነት ለሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ!" በሚል መሪ 14ኛው የብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፣የአዲስ አበባ ከተማ አፈጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልቃድር፣የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተከብሯል ።

ቀኑ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ ሁሉም መንግስታዊና መንግታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ በትምህርት ቤቶች ፣በወታደራዊ ካምፖች ፣ኤምባሲዎች እና በሌሎች ተቋማት ሰንደቅ ዓላማ በመስቀል ተከብሮ ውሏል።

Share this Post