የአፍሪካ የኢትዮጵያና የአዲስ አበባ ፓርኮች እድሳታቸውን አጠናቀው በአዲስ መልክ አገልግሎት መስጠት ይጀምራሉ ።

 

ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሚሳተፉበት የተለያዩ ዝግጅቶች በከተማችን አዲስ አበባ በድምቀት መከናወናቸውን የቀጠሉ ሲሆን ዛሬ ጠዋት የአብርሆት ቤተመፅሀፍት የተመረቀ መሆኑ ይታወሳል በአሁን ሰዓት ደግሞ በክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አማካኝነት የአፍሪካ ፓርክ እየተመረቀ ይገኛል።

የአሁኑን የአፍሪካ ፖርክን ጨምሮ የኢትዮጵያ እና የአዲስ አበባ ፓርኮችንም ከዛሬ ጀምሮ ለህዝብ ክፍት በመሆን አገልግሎት የሚሰጡ ይሆናል።

በቦታው የተለያዩ ታሪካዊ፣ ባህላዊና አገራዊ ዝግጅቶች ለጎብኚዎች እየቀረበ ሲሆን የመዝናኛ ፕሮግራሞችም ተዘጋጅተዋል።

Share this Post