23
Aug
2021
ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በከተማዋ የሚስተዋለውን የምርቶች የዋጋ ንረት ለመከላከል እና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል ከንግዱ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት በማካሄድ ላይ ይገኛሉ ።ከሁሉም ክፍለከተሞች የተውጣጡ አስመጪና ላኪዎች ፣አከፋፋዮች እና የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት የውይይት መድረክ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።"ወቅቱ ከትርፍ በላይ ሀገር እና ህዝብ ስለማትረፍ የምናስብበት ነው" በሚል የኑሮ ውድነቱን ለማቃለል ከንግዱ ማህበረሰብ ምን ይጠበቃል ፣ መንግስትስ መውሰድ ያለበት እርምጃ ምን መሆን አለበት በሚሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት በመካሄድ ላይ ነው።