03
May
2022
በዛሬው እለትም ታላቁን የኢድ ሰላት ለማከናወን ህዝበ ሙስሊሙ በተሰባሰበበት ወቅት እኩይ ሴራቸውን ለመተግበር በሰማዕታት ሃዉልትና በመስቀል አደባባይ በተደረገ ሙከራ በንብረት እና በፀጥታ ሃይሎች ላይ መጠነኛ ጉዳት ቢደርስም በሰላም ወዳድ ሙስሊም ወገኖቻችን ብርቱ ጥረትና በፀጥታ ሃይሎች ቅንጅት የትርምስ ፍላጎቱና ዕቅድ ሙሉ ለሙሉ ከሽፏል ለዚህ እንኳን ደስ አላችሁ ።
ህዝበ ሙስሊሙም በሁሉም አካባቢዎች ሶላቱን ፈፅሞ ወደየአካባቢውና በሰላም ተመልሷል።
ወደፊትም በከተማችን አዲስ አበባና በመላው ሃገራችንን ሰላም ለማደፍረስና አንድነታችንን ለመበተን በሚፈልጉ የዉስጥ ባንዳዎችና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ላይ የማያዳግም እርምጃ የሚወስድ መሆኑን ከወዲሁ እናረጋግጣለን።"