ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጠቅላይ ጽህፈት ቤት እና የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት አባቶች ጋር የጥምቀት በዓል አከባበርን በተመለከተ ውይይት አድርገዋል::

በውይይቱ የጥምቀት በዓል ሃይማኖታዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ በሰላማዊ መንገድ እንዲከበር አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን አባቶቹ የገለፁ ሲሆን ቤተ-ክርስቲያኒቷን የማይወክሉ ንግግሮችን እና ድርጊቶችን ፈፅሞ እንደማይቀበሉና እንደሚያወግዙ ይህንንም ለምዕመናቸው ግልፅ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል::

ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በበኩላቸው በዩኒስኮ በቅርስነት የተመዘገበው የጥምቀት በዓል አከባበር ሃገራዊ ቅርስ እንደመሆኑ በዓሉ ሃይማኖታዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ በሰላም እንዲከበር የሃይማኖት አባቶቹ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል::

የሃይማኖት አባቶቹ የከተማ አስተዳደሩ ለበዓሉ አከባበር የተለመደውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል::

Share this Post