ከዓድዋ ድል ጋር የተያያዙ ቅርሶች በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም

ከዓድዋ ድል ጋር የተያያዙ ቅርሶች በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እንዲቀመጡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ያቀረቡትን ጥሪ በመቀበል የጋምቤላ እና የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት ተወካዮች ዛሬ በእጃቸው የሚገኙ ቅርሶችን ለከተማ አስተዳደሩ አስረክበዋል::

ቅርሶቹን የተረከቡት የከንቲባ ጽ/ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቁ ቅርሶቹ ትውልድ የሚማርባቸው ጎብኚዎችና ተመርማሪዎች የሚመራመሩባቸው በመሆናቸው በመታሰቢያ ሙዝየሙ እንዲቀመጡ ሁለቱ ክልሎች ስላበረከቱ በከተማ አስተዳደሩ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል::

Share this Post