የአ/አበባ ምክር ቤት የተለያዩ ሹመቶችን አፀደቀ

 

3ኛው የአዲስ አበባ ምክር ቤት 2ኛ አመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሂደ ያለው የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ያቀረቡትን የተለያዩ የሥራ ሃላፊዎችን ሹመት አጽድቋል::

በዚሁ መሰረት

1. ዶ/ር ቀነዓ ያደታ 👉 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ

2. አቶ ምትኩ አስማረ 👉 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ

3. ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ 👉 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ

4. ወ/ሮ ሃቢባ ሲራጅ 👉 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ

5. ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር 👉 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር

6. አቶ ጀማል ረዲ 👉 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር በመሆን ፀድቀዋል።

 

 

Share this Post