የሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት እድሳቱ ተጠናቆ ተመረቀ

 

ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት እድሳቱን ጨርሶ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።

በ1927 ዓ.ም እንደተመሰረተ የሚነገርለትና በርካታ አንጋፋ ከያንያንን ያፈራው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት አሁናዊ ገፅታውን ይዞ እንዲሰራ የተደረገው በ1994 ዓ.ም ነበር።

ይህን ገፅታውን በጠበቀ መልኩ በ2013 ዓ.ም የተጀመረው የቴአትር ቤቱ የእድሳት ስራ ተጠናቆ በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት ክፍት መደረጉን ከአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Share this Post