አካል ጉዳተኛ መሆን ለድህነት ምክንያት አይሆንም

አቶ ጃንጥራር አባይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የከተማው የስራ ኢንተር ፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በዛሬው እለት 35 በአካል ጉዳተኞች ለተደራጁ ኢንተርፕራይዞች የመስሪያ ቦታ በማመቻቸት ቁልፍ አስረክቧል፡፡

በከተማው 400 በላይ ስራ አጥ ዜጎችን ስራ ለመፍጠር እየተሰራ ነው ያሉት ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ ከእነዚህ ውስጥም አካል ጉዳተኞች አሉበት እነሱን የሚመጥን የመስሪያ ቦታም ለማሰናዳት መንግስት ጥረት እያደረገ ነው የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደግሞ መንገዱን በመጀመር በዛሬው እለት የመስሪያ ቦታ ለማስረከብ ባደረገው ዝግጅት ላይ ተገኝተን ደስታችሁ ተካፋይ በመሆናችን ደስተኛ ነን ብለዋል፡፡

በክፍለከተማው የቦታ እጥረት ቢኖርም ለእናንተ ይህን ቦታ ማመቻቸት በመቻሉ አንደከተማ አስተዳደር ትልቅ ክብር አለን ያሉት ምክትል ከንቲባው በተሰጣችሁ ቦታ አምራች በመሆን ቦታውን በአግባቡ በመጠቀም እራሳችሁን ልትለውጡ ይገባል ብለዋል፡፡

ከተማው ውስጥ በመስሪያ በቦታዎች ያልተገባ ልምድ አለ ያሉት አቶ ዣንጥራር ይህም ቦታውን በመስሪያነት ምነግስት ይሰsጣል የተሰጠው አካልም ለሌላ ያከራያል ደግሞ የከተማዋን እድገት ከመጎተቱም በላይ ያከራየውም አካል በምንም አይጠቀምም ይህን አስተሳሰብ እናንተ ጋር ፈጽሞ መታየት የለበትም ሲሉም አፅኖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡

ክፍለ ከተማው 31 ስራ አጥ ዜጎችን ወደ ስራ ለማስገባት በበጀት አመቱ አቅዶ እየሰራ ነው ያሉት ደግሞ የክፍለከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ብሩክ ናቸው፡፡

ከእነዚህም ውስጥ አካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ ማድረግ ስላለብን በዛሬው እለት 120 አካል ጉዳተኞች 20 ለሚሆኑ ደግሞ ከስደት ተመላሾች ይህን ቦታ ማመቻቸት ተችሏ ብለዋል፡፡ ክፍለከተማው የቦታ እጥረት ያለበት ቢሆንም ባለው ልክ ሁሉንም እኩል ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራም ነው ብለዋል ዶክተር ብሩክ

አካል ጉዳተኞች በከተማው በርካታ ቁጥርን የያዙ ቢሆኑም በቁጥራቸው ልክ ተጠቅመዋል አይባልም ያሉት ደግሞ የከተማው ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ለና የሺንጉስ ናቸው፡፡ አካል ጉዳተኝነት ፈጽሞ ከስራ አያግድም ያሉት ዶክተሯ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለእነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች የሚሆን ቦታ አዘጋጅቶ በዛሬው እለት ቁልፍ ለማስረከብ መብቃቱ ለለውጥ በኩል ደረጃ በማሰብ መንቀሳቀሱን የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡

በዛሬው እለት 34 ኢንተር ፕራይዞች 93 አንቀሳቃሾችአካል ጉዳታቸው ሳያግዳቸው ተደራጅተዋል እኛም የመስራት ፍላጎታቸውን አይተን ቦታ አመቻችተን ቁልፍ አስረክበናል ያሉት በክፍለከተማው ምክትል ስራ አስፈጻሚና የስራ ኢንተር ፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ፅህፈት ሀላፊ ወይዘሮ ነኢመተላህ ከበደ የተደራጁትም በቆዳ፣ በልብስ ስፌትና በአገልግሎት ላይ ይሰራሉ ብለዋል፡፡

Share this Post