በ2015 በጀት ዓመት ከ33ሺ በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ስልጠና ለመስጠት ዝግጅት ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ቴክኒክ ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡

2013/2014 . 12 ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ወስደው በተለያዩ ኮሌጆች ስልጠና ያላገኙ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክ ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አስታውቋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክ ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ / ሀቢባ ሲራጅ እንደገለጹት የመማሪያ ክፍልችን እና ኮሌጆችን ለስልጠናው ምቹ ለማድረግ የህንጻ እድሳት እና የማሽነሪዎች ጥገና በማድረግ 2015 በጀት ዓመት 12 ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ወስደው በተለያዩ ኮሌጆች ስልጠና ያላገኙ 33 189 ተማሪዎችን ተቀብለው ለማስተማር ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

የቢሮው ኃላፊዋ / ሀቢባ ሲራጅ 2013/2014 . 12 ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች 2014 በነበረው የመቁረጫ ነጥብ መሰረት እንደሚስተናገዱም ነው የገለጹት፡፡

ሰልጣኝ ተማሪዎች ከደረጃ 1 አስከ ደረጃ 5 በተለያዩ 14 ኮሌጆች እድገት ተኮር በሆኑ 124 የሙያ ዘርፎች የሙያ ስልጠና ይሰጣልም ተብሏል፡፡

ስልጠና የሚሰጣቸው ተማሪዎች ከዚህ በፊት 12 ክፍል አጠናቀው ቤታቸው የተቀመጡ ተማሪዎች ሲሆኑ ሴት ተማሪዎች በዚህ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ከስልጠና በኃላ የስራ እድል እንዲፈጠርላቸው እንደሚደረግም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክ ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ / ሀቢባ ሲራጅ ተናግረዋል፡፡

የቢሮው የስልጠና ልማት ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታደለ አየነው በበኩላቸው በተፈጥሮ ሳይንስ እና በማህበራዊ ሳይንስ 12 ክፍል የመቁረጫ ነጥቡን የሚያሟሉ ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጆች ስልጠና እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል፡፡

Share this Post