"በወንጪ ዳንዲ ኢኮ ቱሪዝም መንደር ግንባታ ከ8,000 እስከ 12,000 ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል"ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ

ወንጪ ሁሌም ንፁህ የተፈጥሮ ስጦታ ሆና ቆይታለች። የተፈጥሮን ድንቅ በረከት ተቀብሎ ተንከባክቦ እና አበልፅጎ መጠቀም ደግሞ የኛ የሰውልጆች ተጠባቂ ተግባር ነው።

የወንጪ ዳንዲ ኢኮ ቱሪዝም መንደርን በማልማት ሂደት በግንባታው ምዕራፍ ከ8,000 እስከ 12,000 ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል። ግዙፍ የመሰረተ ልማት ስራ ተሰርቷል።

43 ኪ.ሜትር መንገዶች፤ 35ኪ. ሜትር የመንገድ መብራት እና የኃይል አቅርቦት፤ 72 ሜትር ድልድይ እና ትምህርት ቤት ተጠቃሽ ናቸው። የአካባቢው ወጣቶች ታላላቅ የልማት ስራዎች ይዘው የሚመጡትን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማጣጣም ጀምረዋል። ሰፊው የአካባቢው ማኅበረሰብም አሁን የላቀ የተጠቃሚነት ዕድል አግኝቷል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

ለተጨማሪ መረጃ፦

👉 YouTube https://www.youtube.com/channel/UCagI4q5d_EtvTsajRXWnFjA

👉 Tik Tok= https://www.tiktok.com/@aacommu

👉 Telegram https://t.me/AAcommu

👉 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=100066583024934...

👉 Website https://cityaddisababa.gov.et

Share this Post