በከተማችን ያለውን ውስን የመሬት ሀብት ለተገቢው ሕዝባዊ አገልግሎት እንዲውል ለማስቻል ፤ ባለፉት 9 ወራት በርካታ ተግባራትን ማከናወን ተችሏል

 

➡️ 101 ለሚሆኑ የልማት ጥያቄዎች 74.76 ሄክታር መሬት ሕዝባዊ ጠቀሜታቸውን በመለየት በካቢኔ ውሳኔ በምደባ ምላሽ እንዲያገኙ ተደርጓል።

➡️ ለሆስፒታል ግንባታ 24 ቦታዎች ➪ ለሆቴል 12 ቦታዎች

➡️ ከኤምባሲዎች በልዩ ልዩ ምክንያት ተነጥቆ የነበረን 15 ቦታ እንዲመለስላቸው መደረጉ

➡️ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርና ኢንቨስትመንትን በሁለቱ አገራት መካከል ለማሳደግ በማሰብ ለቻይና የባህል ማዕከልና ለቀርቃሃ ሰርቶ ማሳያ የሚሆን በድምሩ 2 ቦታዎች መስጠት መቻሉ

➡️ ልዩ ልዩ ሕዝባዊ ጠቀሜታ ላላቸው ኢንዱስትሪዎች 16 ቦታዎችን

➡️ ለባንኮች የግንባታ ቦታ ➪ ለትምሕርት ተቋማት 2 ቦታዎችን

➡️ የከተማችንን የቤት ፈላጊዎች ተደራሽ ለማድረግ እንዲቻል ለሪል እስቴት አልሚዎች 6 ቦታዎችን

➡️ በአጠቃላይ በ2013 በጀት ዓመት ማስተናገድ ከተቻለውን የመሬት አቅርቦት ጥያቄን ባካተተ መልኩ መሬት ማቅረብ ተችሏል።

➡️ ከዚሁም ጋር በተጓዳኝ 13 ሄክታር መሬት ለጨረታ ለማቅረብ የቅድመ ዝግጅት ስራም ተጠናቋል ።

➡️ በሕገ ወጥ መንገድ በወረራ የተያዘ 383.3 ሄክታር መሬት በማጣራት ለመሬት ባንክ ተመላሽ ማድረግ እንዲሁ ተከናውኗል።

➡️ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሌብነትና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ብሎም የመሬት ዝርፊያን በተመለከተ ተጠያቂነትን ለማስፈን በርካታ አበረታች ተግባራትን ማከናወን ተችሏል:

➡️ አስቀድሞ ባልተገባ አግባብ የተሰራጨን ካርታን በማምከን ከ450ሺ በላይ የመሬት ካርታን በአዲስ መልክ እንዲቀየር በማድረግ በፎርጂድ ሲታተም የነበረን የመሬት ካርታን ማስቆም ተችሏል።

➡️ በአርሶ አደሮች ስም በደላሎችና ፣ማንነታቸው ለግዜው ባልተረጋገጠ አካላት የወጣን 2 ሺ 170 ካርታ በማጣራት 497 ይዞታዎች (207 ሺ ካሬ ሜትር መሬት)በሕገ ወጥ መንገድ እንዲያዙ የተደረጉ መሆኑ በመረጋገጡ እርምጃ መውሰድ ተችሏል ።

➡️ በሕገ ወጥ የመሬት ወረራ የተሳተፉ በከተማ አስተዳደር እስከ ወረዳ ባሉ መዋቅሮች የሚሰሩ 243 አመራሮችና ሠራተኞች ( 155 የመንግሥት የስራ ኃላፊዎችና 88 ባለሙያዎች) ላይ ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል።

➡️ መሬት ውስንና ቁልፍ ሃብታችን በመሆኑ ይህንን ውስን ሃብት በአግባቡ ለማስተዳደር የአሰራር ሥርዓተን ማሻሻል ፥ ዘመናዊ አገልግሎትን መዘርጋት ፥ ተጠያቂነትን ማስፈን ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው‼️

Share this Post