07
Jun
2022
የአዲስ አበባ ከተማ ከአለም የC40 አባል ከተሞች መካከል አንዷ ስትሆን በቅርቡ በአፍሪካ ውስጥ የC40 ከተሞች የንፁህ አየር መግለጫ (The C40 Clean Air Cities Declaration in Africa)
በሚል የተጀመረዉን አዲስ ፕሮግራም ለማስኬድ በአፍሪካ ቃል ከገቡ አስር (10) የC40 ከተሞች መካከል አንዷ ናት።
ከተማዋ የአየር ጥራቷን የአለም ጤና ድርጅት ካስቀመጠዉ የአየር ጥራት ደረጃ አንፃር ለማስጠበቅ እያከናወነች ባለው ስራ የC40 የአየር ንብረት አመራር ቡድን (C40 Climate Leadership
Group) ክቡር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ላበረከቱት አስተዋኦ ያላቸዉን ከፍተኛ አድናቆት ገልፀዋል፡፡