6ኛው የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን መክፈቻ ስነ-ስርዓት የጋራ ስብሰባ መካሄድ ጀመረ

 

6ኛው የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን መክፈቻ ስነ-ስርዓት የጋራ ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል።

በዚህም 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን የጋራ መክፈቻ ሥነ-ስርዓት ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚደንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ የ2015 ዓ.ም ዋና ዋና የመንግስት አቅጣጫዎችን የሚያመላክት ንግግር እያደረጉ ይገኛል።

በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የሁለቱም ምክር ቤቶች አባላት ተገኝተዋል።

በመርሐ ግብሩ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

 

 

 

 

Share this Post