8ኛው የአፍሪካ የትምህርት ምገባ ቀን

የተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት የትምህርት ሚኒስትሮች የዓለም የምግብ ፕሮግራም ኃላፊዎች የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና የትምህርት ኮሚሽነሮች እንዲሁም የተለያዩ ሃገራት የምገባ ኤጀንሲዎች በተገኙበት በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ አክብረናል::

ትላንት ስንጀምረው ቀላል ይመስል የነበረው የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም ዛሬ ላይ አድጎ እና አለምአቀፍ እውቅናን አግኝቶ የተለያዩ ሃገራት ልምድ የሚወስዱበት ስራ በመሆኑ እጅግ ደስ ይለናል::

አሁንም ትውልድ የመገንባት ስራችን በማጠናከር ለተማሪዎቻችን ምግብ ብቻ ሳይሆን ፍቅርንም እየሰጠን ሃገሩን የሚወድ ጠንካራ ዜጋ የማፍራት ስራችንን እንቀጥላለን::

ከንቲባ / አዳነች አቤቤ

 

Share this Post